News >> Breaking News >> FanaBC
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በጎንደር ከተማ የሚገኘው የዳሽን ቢራ ፋብሪካ በ1 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ ያስገነባው የማስፋፊያ ፕሮጀክት በዛሬው ዕለት ተመርቋል፡፡ በምረቃ ስነ ስርዓቱ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ዶክተር ይልቃል ከፋለ፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር እና ሌሎች የፌዴራል፣ የክልል […]
The post ዳሽን ቢራ ፋብሪካ በ1 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር በላይ በጎንደር ያስገነባውን የማስፋፊያ ፕሮጀክት አስመረቀ appeared first on Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C.
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ዛሬ በተካሄደው የፋና ላምሮት ምዕራፍ 10 የፍጻሜ ውድድር ድምፃዊት ያለምወርቅ ጀምበሩ አሸነፈች፡፡ በውድድሩ ምዕራፍ የመጨረሻ ዙር የቀረቡት ድምፃውያን ዳንኤል አዱኛ ፣ ደሳለኝ አበበ፣ያለምወርቅ ጀምበሩ እና ገረመው ገብረፃዲቅ በሦስት ዙር የሙዚቃ ዝግጅታቸውን ለዳኞችና ለተመልካቾች በቀጥታ አቅርበዋል፡፡ ዳኞችም በተቀመጡ መስፈርቶች መሰረት የየራሳቸውን ነጥብ የሰጡ ሲሆን፥ ያለምወርቅ ጀምበሩ […]
The post በፋና ላምሮት የድምፃውያን ውድድር ያለምወርቅ ጀምበሩ አሸነፈች appeared first on Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C.
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የምግብ እርዳታ የጫኑና እስካሁን ከተላከው ከፍተኛውን መጠን የያዙ 308 ተሽከርካሪዎች በዚህ ሳምንት ትግራይ ክልል መግባታቸውን የዓለም ምግብ ፕሮግራም አስታወቀ። የዓለም ምግብ ፕሮግራም በኢትዮጵያ በማህበራዊ ትስስር ገጹ እንዳስታወቀው÷ በዚህ ሳምንት እስካሁን ወደ ትግራይ ክልል ከተላከው ከፍተኛ የሆነውና የምግብ እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ተጨማሪ 800 ሺህ ሰዎች ተደራሽ የሚሆን ሰብዓዊ […]
The post የሰብዓዊ እርዳታ የጫኑ ተጨማሪ 308 ተሽከርካሪዎች ትግራይ ገቡ appeared first on Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C.
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ የአፍሪካ ኅብረት የልማት ኤጀንሲ ዋና ሥራ አሥፈፃሚ ወይዘሮ ናርዶስ በቀለን በፅሕፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል፡፡ ከንቲባ አዳነች ለአፍሪካ ኅብረት የልማት ኤጀንሲ ዋና ሥራ አሥፈፃሚ ወይዘሮ ናርዶስ የሀገሪቱን የለውጥ እንቅስቃሴ በተለይም በመዲናዋ እየተከናወኑ ያሉ የለውጥና የሪፎርም ስራዎች ስላሉበት ደረጃ ማብራርያ ሰጥተዋል፡፡ […]
The post ከንቲባ አዳነች ከአፍሪካ ኅብረት የልማት ኤጀንሲ ዋና ሥራ አሥፈፃሚ ጋር ተወያዩ appeared first on Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C.
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሶማሌ ክልል ገቢዎች ቢሮ በክልሉ በ2014 በጀት ዓመት የሥራ አፈፃፀም በከፍተኛ ግብር ከፋይነት የተመዘገቡ ግንባር ቀደም ግብር ከፋዮችን ሸለመ፡፡ በሶማሌ ክልል ገቢዎች ቢሮ አዘጋጅነት በ2014 በጀት ዓመት ግንባር ቀደም ከፍተኛ ግብር ከፋዮችን ለመሸለም የተዘጋጀው ሥነ- ሥርዓት በጅግጅጋ ከተማ ፣ ቀርያን ዶዳን መሰብሰቢያ አዳራሽ ነው የተካሄደው፡፡ በዝግጅቱ ላይ […]
The post የሶማሌ ክልል በ2014 በጀት ዓመት ግንባር ቀደም ያላቸውን ከፍተኛ ግብር ከፋዮች ሸለመ appeared first on Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C.
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4 ፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ለ3 ሺህ 673 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ አድርጓል፡፡ የክልሉ መንግስት ጉዳዩን አስመልክቶ ዛሬ ባወጣው መግለጫ÷ ለሕግ ታራሚዎቹ ይቅርታ የተደረገው በ1994 ዓ.ም ተሻሽሎ የወጣው የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ ሕገ መንግሥት አንቀፅ 57(3) (i) እና የይቅርታ ሥነ ስርዓት ማስፈጸሚያ አዋጅ ቁጥር 114/1998 አንቀፅ 12(2) ለክልሉ መንግሥት […]
The post የኦሮሚያ ክልል ለ3 ሺህ 673 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ አደረገ appeared first on Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C.
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ለሚቀጥሉት አምሥት ወራት የመኖሪያ ቤት አከራዮች በተከራዮቻቸው ላይ ምንም ዓይነት የዋጋ ጭማሪም ሆነ ከቤት የማስለቀቅ ተግባር እንዳያደርጉ ውሳኔ አሳልፏል ። የድሬዳዋ አስተዳደር ካቢኔ ሰኔ 2 ቀን 2014 ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ ሁለት ውሳኔዎችን ያሳለፈ ሲሆን ፣ ውሳኔዎቹን አስመልክቶ የአስተዳደሩ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ […]
The post ለሚቀጥሉት 5 ወራት የቤት ኪራይ ዋጋ ጭማሪም ሆነ ተከራዮችን ማስለቀቅ የተከለከለ ነው – የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር appeared first on Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C.
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4 ፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአማራ ክልልርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፋለ የመገጭ ግድብን እየጎበኙ ነው። በጉብኝት መርሐ ግብሩ የመገጭ ግድብ ግንባታ ሂደት የዛሬ ሁለት ዓመት ይጠናቀቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተመላክቷል፡፡ በ5 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር እየተገነባ ያለው ይህ ግድብ ከመስኖ ልማት ባሻገር የጎንደር ከተማ የንጹህ መጠጥ ውኃ ችግርን በዘላቂነት ይፈታል ተብሎ ተስፋ የተጣለበት […]
The post ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፋለ የመገጭ ግድብን እየጎበኙ ነው appeared first on Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C.
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4 ፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሲሚንቶ ግብይትን እያዛቡ ያሉት አከፋፋዮችና ቸርቻሪዎች ከግብይት ውጪ መደረጋቸውን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር አቶ ገብረ መስቀል ጫላ በሰጡት መግለጫ÷በግንባታው ዘርፍ ዋነኛ ግብዓት የሆነው ሲሚንቶ ግብይቱ ኢኮኖሚያዊ ባልሆኑ ሰውሰራሽ ምክንያቶች እየተዛባ ዋጋውም ከጊዜ ወደጊዜ እየናረ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ ለግብይቱ ችግር ውስጥ መውደቅ […]
The post የሲሚንቶ ግብይትን እያዛቡ ያሉት አከፋፋዮችና ቸርቻሪዎች ከግብይት ውጪ ተደረጉ appeared first on Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C.